በዎላይታ ዲያስፖራ ማህበራት (AWANA, WIDA and WCWDC) ትብብር የሚካሄድ የድጋፍ ማሰባሰብያ

ይህ በወላይታ ሶዶ ከተማ መርካቶ ገበያ እሁድ ታህሣሥ 11 ቀን 2013 ዓ.ም ከጧቱ 1፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 6፡00 ሰዓት በደረሰው መነሻው ባልታወቀውና በዓይነቱ ከፍተኛ የሆነው የእሳት ቃጠሎ አደጋ ሀብት ንብረታቸውን ላጡ ወገኖቻችን በውጭ ሃገራት  ነዋሪ ከሆኑ የአካባቢው ተወላጆችና ወዳጆች የድጋፍ ማሰባሰብያ ሲሆን በዚህ አዉዳሚ አደጋ የተጎዱ ዎገኖቻችንን ለማቋቋም ሁላችሁም ለወገን ደራሽና አለኝታነታችሁን በማሳየት ድጋፍ እንድታደርጉ በታላቅ አክብሮትና ፍቅር እንጠይቃለን።

የሚሰበሰበዉም ገንዘብ ለዚሁ አላማ በዞኑ አስተዳደር ወደተከፈተዉ የባንክ አካንት ገቢ የሚደረግ መሆኑን ለማረጋገጥ እንወዳለን።

https://charity.gofundme.com/o/en/campaign/fund-raising-on-the-fire-disaster-victims-in-wolayta-sodo

Leave a comment