ባለፈው ቅዳሜ December 5, 2020 የማኅበራችን ጠቅላላ ስብሰባ መደረጉ ይታወሳል። የጠቅላላ ጉባዔው ያለፈውን ዓመት ክንውኖችን በመገምገምና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ምክክር በማድረግ ውሳኔዎችን በማስተላለፍ ነበር የተጠናቀቀው።
በስብሰባው ላይ በመገኘት ከፍተኛ ተሳትፎ ላሳያችሁ አባሎቻችንና ደጋፊዎቻችን ሁሉ ያለንን አድናቆት በዚሁ አጋጣሚ እየገለጽን ለትውልድ አካባቢያችን ልማት፣ ማኅበራዊ ለውጥና ዕድገት የበኩላችሁን ድርሻ ለመወጣት በቀጣይነት ለምታሳዩት ፈቃደኝነትና መሰጠት ምሥጋናችን የላቀ ነው።
በስብሰባው ከተከናወኑት ተግባራት አንዱ የማኅበሩን ሥራ አስፈጻሚ አባላትንና የተለያዩ ዘርፍ መሪዎችን መምረጥ ነበር። በዚሁ መሠረት ከዚህ በታች ስማቸውና የሥራ ድርሻቸው በዝርዝር የተጠቀሰ ወንድሞችና እህቶች በጉባዔው የተመረጡ መሆኑንና እስከ ቀጣይ የምርጫ ዘመን ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ አደራ የተሰጣቸው መሆኑን ስንገልጽ በታላቅ ደስታ ነው።
በመሆኑም:- ተመራጮች ሁላችንም በዚሁ ታሪካዊ ወቅት የተጣለብንን ሕዝባዊ አደራና ኃላፊነት ቸል ሳንል በታማኝነትና በቁርጠኝነት በመወጣት ለሕዝባችን ባለውለታነታችንን በተግባር እንድንገልጽ ይሁን።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦቿን ይባርክ!!



AWANA