ልማታዊ ባለሀብት አቶ አበበ ዘለቀ በመሞታቸው የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

ልማታዊ ባለሀብት አቶ አበበ ዘለቀ በመሞታቸው የተሰማንን ጥልቅ ሐዘን እየገለጽን ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እንመኛለን።

አቶ አበበ ትጉህ ሠራተኛ፣ ለሰው አሳቢ፣ ትሁትና ገር አገር ወዳድ ሰው እንደነበሩ በቅርበት የሚያውቋቸው ይመሰክራሉ። አቶ አበበ ዘለቀ በወላይታ የሠሯቸው የልማት ሥራዎች የእጃቸው አሻራ ሆነው በማኅበረሰቡ ዘንድ ይኖራሉ።

አቶ አበበ በከተማዪቱ በሠሯቸው የገበያ ማዕከልና በዘመናዊ ሆቴል ብቻ ሳይሆን በሌሎችም ልማታዊ ሥራዎች ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል የመፍጠር ዕቅድ እንደነበራቸው ይነገራል።

እሳቸው ቢሞቱም ታሪካቸው አይሞትም። በሰሜን አሜሪካ የወላይታ ተወላጆችና ወዳጆች ማኅበር እኚህን የልማት አርበኛ ለተነጠቀው የወላይታ ማኅበረሰብ ሁሉ መጽናናትን ይመኛል።

AWANA

Leave a comment